ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሌዎ 14ኛ የብፁዕ አቡነ ብርሃነኢየሱስ ለቅድስት መንበር ያቀረቡትን ከኃላፊነት የመነሳት ጥያቄ ተቀበሉ

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ እና የአዲስ አበባ ሀገረሰብከት ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ብርሃነኢየሱስ በጡረታ ምክንያት ሐዋርያዊ ኃላፊነታቸውን አሰረከቡ።

ለቅድስት መንበር ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሌዎ 14ኛ በዛሬው ዕለት ጥያቄያቸውን መቀበላቸውን በቅድስት መንበር ልዪ መልዕክተኛ ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ አማካይነት ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ይፋ ተደርጓል።

የብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ ተተኪ በመሆን የአዲስ አበባ ረዳት ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ተስፋስላሴ የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ ሆነው ተሹመዋል።


Leave a Reply

“በነፃ የተቀበላችሁት በነፃ ስጡ”

ማቴዎስ 10፡7-15

አስተንትኖ፡ የሚስዮናዊ ደቀመዝሙርነት ራስን መቻልን፣ መተማመንን እና ልግስናን ይጠይቃል። የተላክነው ለጥቅም ሳይሆን የምስራቹን ቃል ለማወጅና ለመባረክ ነው።

    The Catholic Bishops Conference of Ethiopia (CBCE)
  • Wawel Street, Besides of Catholic Cathedral, Piassa
  • CBCE@cbce-gs.org
  • scpr@eccsdco.org
  • +251-11-1550300